2014 ኤፕሪል 7, ሰኞ

ሰበር ዜና- በጎንደር ከተማ የ3 ሽህ ሰዎች መኖሪያ ቤት ይፈርሳል!!

በጎንደር ከተማ በህገ ወጥ መልኩ ተገንብተዋል የተባሉ ከ3 ሺህ በላይ መኖሪያ ቤቶች ሊፈርሱ ነው፡፡ ቤቶቹ በተለምዶ የጨረቃ ቤት ናቸው በሚል ሰበብ የሚፈርሱ ሲሆን እንደ አንዳንድ አስተያዬት ሰጪዎች የቤቶቹ መፍረስ የቤት አልባ ሰዎችን ቁጥር ከፍ እንደሚያደርገው ያምናሉ፡፡ ብዙ ቤተሰቦችም እንደሚፈናቀሉ ይታመናል!! መንግስት ቤቶቻቸው የሚፈርስባቸውን ቤተሰቦች ችግር ከወዲሁ ሊያጤነው እንደሚገባ ማሳሰብ እንወዳለን፡፡